ስለ ቤተ ክርስቲያናችን (About)

የቤተ ክርስቲያናችን አመሠራረት ... 1989 .. ምሮ የተ ቅዱሳን በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በመሠብሠብ የተጀመረ ነው፡፡ በተለያየ ሁኔታ በጀርመን ሀገር ለመኖር ከገር ቤት እና ከተለያዩ ሀገሮች ጌታን የሚያውቁ እና የሚያገለግሉ የነበሩ እየበዙ እንዲሁም አዳዲስ ነፍሳትም እየተጨመሩ ብረቱ ተጠናከረ፡፡ በመሆኑም በሁሉ አቅጣጫ እየሰፋ በቁጥርም እየበዛች በመምጣቷ እ..ሐምሌ 27-30/ 1995 .. የመጀመሪያን ዓመታዊ ታቅ ኮንፈራንስ ከመላው የጀርመን ከተከሚገኙ ብረቶች ጋር በመሰባሰብ በግም500 በላይ የሚሆኑ ቅዱሳንን ተቀብሎ በማስተናገድ በእግዚአብሔር እርዳታ የተሳካ ኮንፈራንስ አድርጋለች። ከዚህም በኋላ የብረቷ የምእመናን ቁጥር መጨመርና የመንፈሳዊ አገልግሎትም እየሰፋ መምጣ ምክንያት በቅቱ በነበሩት የብረቱ መሪዎች ብረቷ በመንግት እውቅና እንዲኖራት ... 1998 .. በጀርመን ሀገር በኑርንበርግ ከተማ በኑረንበርግ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያንበሚል ያሜ ብረትነት ወደ ቤተ ክርስቲያንነት ከፍ እንድትልና መንግታዊ ሕጋዊነትንም እንድታገኝ ሆናለች። እንዲሁም እ... 2000 .. የቤተ ክርስቲያን ምረታ እና የምስጋና በዓል በማድረግ እና በቀጣይም አገልግሎቷን በተደራጀ መልኩ ስታከናውን ቆይታ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከደረሰችበት መንፈሳዊም ሆነ የገንዘብ (Financial) አቅም አን ልዩ ልዩ የአገልግሎት ዘርፎችን በማደራጀት ዲያቆናትን ሽማግሌዎችን እና አንድ ወንጌላዊ በ2010 እንዲሁም ቋሚ በጀት በመመደብ አንድ የሙሉ ጊዜ አገልጋይ የሆነ መጋቢ (ፓስተር) ... 2006 .. ከሌላ ከተማ አምጥታ በጉባ በመጋቢነት ሾማለች።
አሁን የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ ስያሜ “የጸጋው ቃል አማኞች ቤተ ክርስቲያን በኑርንበርግ” በመባል በኑርንበርግ ከተማ እንዲሁም “የጸጋው ቃል አማኞች ቤተ ክርስቲያን በቩርዝቡርግበቩርዝቡርግ ከተማ ሁለተኛ አጥቢያ እና “የጸጋው ቃል አማኞች ቤተ ክርስቲያን በሽቫይንፉርትበሽቫይንፉርት ከተማ ሦስተኛ አጥቢያ በመትከል ቅዱሳንን ታገለግላለች፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በታላቁ ተልዕኮ አገልግሎትም ወደ ብዙዎች ወንጌል እያደረሰች የምትገኝ ቤተ እምነት ሆናለች፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎቶች በብዝሃ ቋንቋ (አማርኛአፋን ኦሮሞትግርኛ እና ጀርመንኛ) ለብዙዎች ተደራሽ ሲሆን በማኅበራዊ ሚዲያም የእግዚአብሔርን የድነት መልእክት ለሰው ልጆች ሁሉ እያደረሰች ትገኛለች፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን በአሁኑ ወቅት፡ የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን ዐብያተ ክርስቲያናት ኅብረትን ጨምሮ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ዐብያተ ክርስቲያናት ኅብረት በአውሮጳ (Alliance of the Evangelical Ethiopian Churches in Europe) እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን ዐብያተ ክርስቲያናት ኅብረት በጀርመን (Äthiopische Evangelische Christen Gemeinschaft in Deutschland e.V.) አባል ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡

 

 

ስለ እኛ ተጨማሪ

Follow by Email
YouTube